Saturday 25 November 2017

አቶ ለማና አቶ ገዱ

ይህ የአቶ ለማ መገርሳና የአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ንግግር ግዥ ፓርቲው ኢህአዴግ ውስጥ የአንድነት አስፈላጊነትና የኦሮምኛ ከአማርኛ እኩል የሀገር ቋንቋ መሆን ጥቅም (ይህንና ይህን አንብቡ) የሚረዱ ወገኖች እንዳሉ ብቻ ሳይሆን ይህን ጉዳይ ለረዥም ጊዜ ያሰላሰሉበት እንደሆነ ዪገልጻል። አቶ ለማና አቶ ገዱ ለንግግሮቻቸው ሊመሰገኑ ዪገባል።፡ ያንጸባረቁት አቋም ጥሩና ተስፋ ሰጭ ነው።

ሆኖም ወደ ተግባር ስንሄድ ይህን ልውጦች፤ አንድነት፤ መልካም አስተዳደር፤ ህብረተሰባዊ መሻሻሎች ብተለይ በወጣቶች ስነ መግባር ዙርያ፤ የወላጅና የሃይምናኦት መሪዎች በልጆቻችን ጤንነትና ደህንነት ሃላፊነታቸውን መዋጣት፤ ወዘተ አቶ ለማና አቶ ደጉ ሊፈጹሟቸው ይችሉ ይሆን?

አይችሁሉም ወይም እጅግ ይቸገራሉ አንዳንድ መሰረታዊ መዋቀራዊ ለውጦች ከሌሉ። እነዚህ ችግሮች ዛሬ ያሉት በግለሰብ ድክመቶች ብቻ ሳይሆኑ በመዋቅር ድክመት ነው። በተለይ የአውራ ፓርቲ ፖለቲካ ስርአት ለውቶችን እጅግ አፍኗል። ሌላው በዋንነት ሁለተኛው ችግር በኢህአዴግ ውስጥ የህወሃት የበላይነት መጠን ነው። እነዚህ ሁለቱ ነገሮች በመጠኑ መስተካከል አለባቸው።

የመጀመሪያውን ለማስተካከል ለባለስጣን («ህዝብ ተወካይ») ምርጫዎችን በመጠኑ ነጻ መደረግ አለበት። ሙሉ ነጻነት እንደማይሆን፤ ከአውራ ፓርቲ አገዛዝ ጋር እንደሚቃረን እረዳለሁ። ግን አውራ ፓርቲ 100% ማለት አይደለም።  100% ይባለስጣን ችለተኝነት ያመጣል። ቢሰርቅም ስልጣኑን ለማይሆን ነገሮች ቢጠቅምም ምንም አይደርስብኝም ብሎ። ግን ከስልጣን መውረድ የተወስንም ቢሆን እድል እንዳላቸው ሲረዱ ጥንቃቄ ይጨምራሉ። ስለዚህ ከ 100% ወደ 80 ወይም 70ም አስፈላጊ መሰለኝ።

ሁለተኛው ጉዳይ ይከብዳል። ከብአዴን ኦህዴድና ሌሎቹ ጅግንነትም ብልጠትም ይጠይቃል። ከህዝባቸው ጋር ያላቸውን ቅርበት ማጠናከር ግድ ነው። ይህ ነው ኢህአዴግ ውስጥ ስልጣናቸውን የሚጎለብተው። አሁንም ላለፉት ሶስት ዓመታት የዚህን ፍንጭ እያየን ነው ነገር ግን መጠንከር አለባቸው። መልካም አስተዳደር ለነሱ የህይወትና ሞት ጉዳይ ነው። መልካም አስተዳደር አቋማችንና ግባችን ነው ብለው ቢይዙትና በዚህ ጉዳይ ቆራጥ ቢሆኑ ከህዝቦቻቸው ጋር አንድነት ያመጣሉ። በዚህ ጉዳይ እጅግ ታላቅ ሳ መሰራት አለበት።

በተዘዋዋሪ ከላይ የጠቀስኩት በሙሉ ይሚቻል ነገር ነው። ደም አያፈስም ጦርነትም አያስነሳም። ትንሽ ብልጠት ብቻይ ነው የሚያስፈልገው። ማንንንም አይጎዳም ከሙስናና ጎጂ አስተዳደር መሪዎች በቀር። አይ፤ ማድረግ የሚቻል ነው።

እግዚአብሔር ይርዳቸው። እኛንም ከዳር ቆመን አንገታችንን ደፍተን የምንታዘበው ወይም የምናጨበችበው የምናዝነውም ከዳራችን ወደ መሃል ገትብተን የመፍትዬው አካል እንድንሆን ይርዳን!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!