Monday 25 September 2023

የብሔርተኝነት ሰለቦች

 ቭላዲሚር ፑቲን እንዳሉት የብሄር ማንነት ሊቀያየር ይችላል። ይህ በሰው ልጅ ታሪክ የተለመደ እና ተፈጥሮአዊ ነገር ነው። የማንም የብሄር ማንነት፤ አዲስ ወይንም ግልገል የብሄር ማንነትም ሊከበር ይገባዋል። ቭላዲሚር ቭላዲሚሮቪች ይንን ያሉት የዩክሬን የብሄር ማንነት በአንጻሩ አዲስ (ወደ 150 ዓመት) ቢሆንም መከበር አለበት፤ በግድ ሩሲያዊ ሁኑ ማለት የለባቸውም ነው።

የዩክሬን ብሔርተኝነት የተጀመረው በ19ኛው ክፍለዘመን ነው የዘመናዊ ብሔርተኝነት ርእዮት አለም አውሮፓን ማቀጣጠል ሲጀምር። በዚህ የቃጠሎ ዘመን ስለተወለደ ብሔርተኝነቱ በአደገኛ መንገድ (trajectory) ጉዞውን ጀመረ። 

ማንኛውም ብሔርተኝነት እነዚህን ባህሪዎች አሉት 1) ጠላት (ጥላቻ) 2) ተረት (myth) 3) ሁሉ ገዥነት (ብሔሩ ከሁሉም ነገር ከሃይማኖቱም በላይ ነው ወይንም ጣኦት ነው)። ለምሳሌ ዘመናዊ (በጃንሆይ ዘመን የተወለደው) የኢትዮጵያ ብሔርተኝነት የጠላቱ መስፈርት በአደዋ ጣልያን ነበር የተሟላው። ተረታችን እስከ ህንድ አገር ገዝተን ነበር ይሚለው ነበር (የዛሬው ግዛት ተገቢ ነው ለማለት)። ሁሉ ገዥነትን በ«አገር የግል፤ ሃይማኖት የጋራ» የሚለው አባባል ተሟላ። ጣልያን የቅርብ ጎረቤት ስላልሆነ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ሽኩቻ እየቀነሰ ስለነበር፤ ኢትዮጵያ እንደገና እስከ ህንድ ልግዛ ስለማትል ጂቡቲንም ስለማትፈልግ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ሃይማኖትን ስላልጨቆነ የኢትዮጵያ ብሔርተኝነት በርካታ ችግሮች ቢኖሩትም ጸንፍ የያዘ አልነበረም ብዙ ወደ ከፋ መንገድ አልሄድም ነበር። ግን ...

በአንጻሩ ግን አንዳንድ ብሔርተኝነቶች የብሔርተኝነት ባህሪዎቻቸውን በከፋና ጸንፍ የረገጠ መንገዶች ያሟላሉ። ዩክሬን አንዱ ምሳሌ ነው። በሃያላን ፖላንድና ሩስያ ስለተከበበች አዲሷ ዩክሬንን የሚያራምዱ ፖለቲከኞች የፖላንድና በተለይ የሩሲያን ጥላቻ የዩክሬን ብሔርተኝነት ምሶሶ አደረጉት። ዩክሬን ከሁሉም ጎረቤት ሃብታም ናት ህስቦቿም ስላቭ (slavs) ሳይሆኑ እንደ ናዚ ጀርማን ፍጹም አርያን (Aryan)  ናቸው ተባለ። በመጨረሻ የሀገሪቷ ስፋት የተለያዩ ህዝቦች፤ ሀንጋሪያኖች፤ ሮሜኒያኖች፤ ፖሊሾች፤ ሩስያኖች፤ ያሉበትን ያጠቃልላል ተባለ።

በነዚህ የዩክሬን ብሔርተኝነት ልሂቃን ጸንፈኛ አቋም ምክንያት ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ዩክሬን የጸንፈኝነትና ጦርነት ቀጠና ሆናለች። የዩክሬን ብሔርተኞች አንዴ ፖሊሾችን፤ አንዴ ሮሜኒያኖችን፤ አንዴ ይህዶችን፤ እንዴ ሩስያዊዎችን ለማጥፋት ሲዠምቱ 150 አመት አሳልፈዋል። የጽንፈኝነት መጠናቸው የሚገልጸው በሁለተኛ የአለም ጦርነት ከናዚ ጀርማን ጋር ወግነው ከጀርመኖቹም በላይ ክፋትና ግድያ መፈጸማቸው ነው። የዩክሬን የፖለቲካ የገዥ መደብ ይሁን ሁሉ ያደረገው በብሔርተኝነት እጅግ ተጠምቆና ሰክሮ ሰባዊነት ሙሉበሙሉ ስለጠፋበት ነው።

የዩክሬን ህዝብ ያሳዝናል። ልሂቃኖቻቸው ማንነታቸውን በጸንፈኝነት እና ክፋት መሰረቱት እና ህዝባቸውን የክፋት ማንነት እስረኛ አደረጉት። ልሂቃኑ ህዝቡ ላይ ከጎረቤቶቹ ጋር በሰላም መኖር የሚችል ህዝብን ከጎረቤቱ ጋር የሚስማማ፤ ጠላት የሌለው፤ ዩክሬን ጣኦቱ ያልሆነ፤ ዩክሬናዊ አይደለም የሚለውን ትርክት ጫኑ በት። እጅግ ያሳዝናል።

ኢትዮጵያውስጥም ይህ አይነት ጸንፈኛ ዘመናዊ ብሔርተኝነት አይተናል ባለፉት 50 አመታት። የህወሓት ብሔርተኝነት አንዱ ግልጽ ምሳሌ ነው። አማራ ጠላት ነው፤ ወርቃማ ዘር ነን፤ ክርስትናም ሙስሊምነትም ከትግሬነት በታች ናቸው፤ ትግሬነት ብቸኛ እምነት/ጣኦት ነው። ይህ የህወሓት የትግራይ ብሔርተኝነት አማራን ብቻ ሳይሆን ኤርትርንም፤ ኦሮሞንም በተለያዩ ወቅቶች ፍጹም ጠላት ብሎ ሰይሟል! ታላቋን ትግራይ በራይ ደረጃ አስቀምጦ ለማስፈጸም ጦርነት አውጇል። ሚስኪን የትግራይን ህዝብ በዚህ ክፉ ርእዮት አለም አፍኖ አስክሮ ገድሎታል። እጅግ ያሳዝናል። 

በኦሮሞ ብሔርተኝነትም እንደዚህ አይነት ጸንፈኛ ባህሪዎች ይታያል። ጠላት፤ አማራ። (አማራ ቢያንስ ለ32 አመት ግን ለ46 አመትም ማለት ይቻላል ስልጣን ይዞ አያውቅም ለስልጣን ታግሎም አያውቅም!)። ተረት፤ ኦሮሙማ (ኦሮሙማ የጥነትና ባህላዊ ሳይሆን ልሂቃን በዘመናዊ መንገድ manufacture ያደረጉት ብሔርተኝነት ነው "Being and Becoming Oromo" )። ሁሉ ገዥነቱ ደግሞ በሃይማኖት ላይ የሚያደርገው ዘመቻ ያሳያል፤ ኦርቶዶክስም ሙስሊምም ኦሮሞ ኦሮሙማ ከሃይማኖቱ በላይ መሆን አለበት ነው። ቄስ/ሼክ ትዛዙን ከኦሮሞ ብሔርተኛ ፖለቲከኛ ነው መቀበል ያለበት!

በመርህ ደረጃ የኦሮሞ ማንነት ተደፋፍኖ ነበር፤ ጭቆና ነበር፤ ማለት ይቻላል። ግልጽ ነው። የኦሮሞ ህዝብ እንደማንኛውም ህዝብ ማንነቱ መከበር አለብት ብቻ ሳይሆን ማንነቱን ለጎረቤቱ ማካፋል አለበት ማለት ይቻላል። ይህ ተፈጥሯዊ ነው ጤናማም ነው። ግን እነዚህ ትክክለኛ፤ ሰላማዊ እና ጤናማ መርህዎች በዘመናዊ ጸንፈኛ ብሔርተኝነት ተጠልፈዋል። የኦሮሞ ጸንፈኛ ልሂቃን ህዝቡን አስሮ ወይ ከኛ ጋር ነህ ወይንም ኦሮሞ አይደለህም ብለውት እጅግ እየጎዱት ነው።

ዘመናው ብሔርተኝነት አደገኛ ነው በቀላሉ ወደ ጽንፈኝነት ማየል ስለሚችል። ይህን recognize ማድረግ አለብን። የልሂቃን ሚና ከባድ እንደሆነ መረዳት አለብን። የሚመጣውን ጸንፈኝነት እንዴት መቅረፍ እንደሚቻልም ማጥናት አለብን። ግን ጸንፈኛ ብሔርተኝነት በጸንፈኛ ብሔርተኝነት አይሸነፍም። Scorthed earth እንደ ማሸነፍ ካልተቆጠረ! ዘዴና ብልህነት ይጠይቃል።


Friday 11 November 2022

ቅራኔአችሁን እንፍታላችሁ!

በተለይ ከ1997 ከቅንጅት ዘመን በኋላ ምእራባውያን ማለትም መንግስታት፤ ኤንጂኦዎች፤ ወዘተ ኢትዮጵያዊያን የግትርነት እና የቅራኔ ማባባስ ባህል አላቸው ብለው ያወሩ ነበር። በአንጻሩ እኛ ምእራባውያን በጠቅላላ የፖለቲካ ስልጣኔ በተለይም በቅራኔ መፍታት conflict resolution ጎበዝ ስለሆንን እናንተን ኢትዮጵያውያን እናስተምራችሁ አሉ። በርካታ ስብሰባዎች ትምሕርቶች በብዙ ገንዘብ ወጪ ተካሄዱ። ውጤቱ....

(በነገራችን ላይ እኔም በግሌ ይህ ባህላዊ ችግር አለን ብዬ አምኜ የፈረንጆቹን እርዳታ እንጠቀም ከሚሉት አንዱ ነበርኩኝ።)

ባህል ውስብስብ ነገር ነው። የእገሌ ባህል እንዲህ ነው የእገሌ ባህል እንዲያ ነው በደፈናው ማለት አይቻልም። ሁኔታዎች ሁሉንም ግለሰብም ቡድኖችንም ይቀይራል። እንሆ እነዚህ የቅራኔ መፍታት ባለሙያዎች ምእራባውያን ዛሬ ትክክለኛ ግትርነት ምን እንደሆነ እያሳዩን ነው። በከንቱ ዓለምን ንዩክሊየር ጦርነት ጫፍ ላይ አድርሰዋልና!

እኛ ኢትዮጵያውያን ወዲህ ወድያ ከማየት እራሳችንን ከምእራባውያን ይሁን ከምስራቃውያን ከማነጻጸር ወደ ራሳችን ተመልክተን በራሳችን እሴቶች ተጠቅመን እራሳችን ላይ ብንሰራ ይበጃል። ከሌሎች ጥሩ ነገር መማር ጥሩ ነው ተፈጥርዋዊም ነው። ግን ብዙ ጊዜ ይህ ከጥሩ ነገር መማር አልፎ ወደ ማነጻጸር ይሻገራል እና ሁለት «ኮምፕሌክሶች» ያሳድራል፤ 1) ሌሎች በደፈናው ይበልጡናል ብሎ ማሰብ 2) የራስን እሴቶችን አለማየት። እና ማነጻጸር አደገኛ ልምድ ይሆናል ከእውነታ እንድንርቅ ያደርገናል። ስለዚህ ብዙ ግራ ከኝ ሳንመለከት ችግራችንን በራሳችን በቂ የሆኑ እሴቶች መፍታት ጥሩ አካሄድ ይመስለኛል።

Friday 4 November 2022

ስለ አማራ ብሔርተኝነት እንሟገት፤ በቅንነት!

ይህን አስመልክቶ መቼ ነው ለህዝብ ይፋ የሆኑ ውይይቶች የሚካሄዱት? ለአምራ ፖለቲካ ጤንነት ግልጽ ውይይት አስፈላጊ ይመስለኛል።

እኔ እንደሚገባኝ የአማራ ብሔርተኞች መሰረታዊ ችግር በእውነታ (reality) ሳይሆን በህልም/ቅዠት  የተመሰረተ ነው። የአማራ ብሔርተኝነት ህልም እንዲህ ነው፤ 

እነ አሳምነው ጽጌ (ነፍሱን ይማር) ወይንም ዛሬ እነ ዘመነ ካሴ በአማራ ብሔርተኝነት ፖለቲካ ተጠቅመው 1) ወልቃይት/ራያን ይመልሱ ነበር 2) ቤኒሻንጉል፤ ወለጋ፤ አዲስ አበባ ወዘተ ያለውን አማራ ይጠብቅ ነበር 3) ፌደራል መንግስት ላይ ከባድ ትጽእኖ ያሳድሩ ነበር 4) አማራ ክልልን ያጎለብቱ ነበር 5) ሀገ መንግስቱን ያስቀይሩ ነበር።

ይህ ከእውነታ እጅግ የራቀ እንደሆነ ግልጽ ነው። ለ50 ዓመት ተደራጅቶ የማያውቅ አማራ በአንድ ሁለት ዓመት ተደራጅቶ ህወሓትን፤ ኦነግን፤ ፌደራል መንግስትን፤ ሱዳንን፤ ምእራባውያንን፤ ግብጽን ሁሉ ሊገጥም ይችላል ብሎ ማሰብ ቅዠት ነው። ሆኖም ስሜተን ስለሚቀሰቅስ እና ተከታይን ስለሚያበዛ የፖለቲካ ነጋዴዎች ይህንን ቅዠት በመሸጥ ለስልጣን ይጠቀሙበታል።

የአማራ ህዝብን ህልውና የሚጠብቅ በእውነታ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አካሄድ ነው። ይህም ህዝቡን በኢትዮጵያዊነት ማደራጀት ነው። ይህ አካሄድ የሚገነዘበው እውነታ ይህ ነው፤ የአማራ ትቅም የሚጠበቀው የመአከላዊ መንግስቱ በአግባቡ ከጠነከረ ነው። በተቃራኔው መአከላዊ መንግስቱ ከደከመ እና የጎሳ ፖለቲከኞቹ ከጠነከሩ አማራ ይጎዳል። ምክንያቱም 1) አማራ በዬ ክልል ተበትኗል እና 2) አማራው ከሌሎች ጎሳዎች የሚለየው ከባድ የትርክት ስራ ተሰርቶበት ጎሰኞቹ የአማራ ጥላቻን የፖለቲካ ንግድ አድርገውታል 3) አማራ በርካታ ታሪካዊ ጠላቶች አሉት። በዚህ ምክንያት የአማራ ህልውና ከመአከላዊ መንግስት ህልውና ጋር የተሳሰረ ነው። ኢትዮጵያዊነት የግዱ ነው።

«ኢትዮጵያዊነትን ሞክረን አልሆንም» የሚሉ አሉ። ይህ አስተያየት የሚመነጨው ከታሪክ አረዳዳት ስህተት ነው። በኃይለ ሥላሴ አገዛዝ ኢትዮጵያዊነት (እንደ nation state) ገና እየተገነባ ነበር። በደምብ ሳይጠነክር እራሱ የኢትዮጵያዊነት ጎራው (በዚህ ውስጥ አማራው ሙሉ በሙሉ የተካተተበት ነበር) ተከፋፈለ እራሱ ላይ አብዮት አስነሳ። የኢትዮጵያዊነት ጎራው ገና ያልተገነባን ኢትዮጵያዊነትን አደከመ ማለት ነው። ደርግ ደግሞ አባባሰው። አብዮቱን ሲያፋፍም የኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራውን (እራሱንም ጨምሮ) ይበልጥ አድክሞ የኃይል ሚዛኑ ተቅላላ ወደ ጎሰኞቹ ጎራ እንዲያመዝን አደረገ። መጨረሻ ላይ ስልጣንን ለጎሰኞቹ አስረከበ። ጎሰኞቹ ሲያሸንፉ አማራ መጎዳት ጀመረ።

ይህ ታክሪክ በግልጽ የሚያስተምረን የአማራ ህዝብ ህልውና ከኢትዮጵያዊነት የተሳሰረ መሆኑ ነው። ለዚህ ነው ለአማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊነት የግድ ነው ያልኩት።

የግድ እንደሆነ ካመንን ቀጥሎ ጥያቄ እንዴት ነው ኢትዮጵያዊነትን ማጠንከር የምንችለው ነው። አዎን እጅግ ከባድ ስራ ነው። ለዚህም ነው አንዳንዱ አይቻልም ብሎ የሚሸሸው። የጎሳ ፖለቲካ የተፋፋመብት ሀገር ውስት ኢትዮጵያዊነትን ማቀንቀን ከጎሰኞቹ እጥፍ ድርብ ብልህነት እና የፖለቲካ ችሎታ ያስፈልገዋል። በዚህ ምክንያት የአማራ ልሂቃን ማተኮር ያለበት ይህ ከባድ ስራ ላይ ነው። ህዝቡን በቀላሉ ስሜት ውስጥ የሚከተው ግን መጨረሻ ላይ ገደል የሚከተው ቀላል ፖለቲካን ትቶ ወደ ከባዱ ግን የግድ የሆነ ኢትዮጵያዊነት ስራ መግባት አለበት። 

የዐቢይ አህመድ መንግስትን መደገፍ እና ውስጡ ሆኖ መስራት አንዱ የዚህ ስራ ስትራቴጂ ነው። መአከላዊ መንግስቱ መጠንከር አለበት። ሀገረ መንግስቱ (nation state) መጠንከር አለበት የጎሰኞቹ ጎራም ይሁን የውጭ ጠላቶችም በቀላሉ ሊያጠቁ እንዳይችሉ። ስለዚህ መንግስት ምንም ችግሮች ቢኖሩት ለምጉዳት ይበልጥ ለማፍረስ መስራት የለብንም። መንግስትን መገንባት ነው ያለብን በተቻለ ቁጥር በኛ ፍላጎት። ይህ ስትራቴጂ የአማራ ህዝብን ይበጃል ብቻ ሳይሆን ለህልውናው የግድ ነው።

ሁለተኛ ስትራቲጂ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር መግባባት የግድ ነው ኢትዮጵያዊነትን ለማጠንከርና ሀገር መንግስቱንም ለማጠንከር። ሰጦ ገብ መቻል አለብን። በሶፍት ፓወር (መገናኛ ብዙሃን በመቋቋም፤ ቋንቋ በመማር፤ ወዘተ) ሌሎች ብሄረሰቦች ላይ መልካም ተጸኖ ማድረግ መቻል አለብን። ጎሰኞቹ አማራን በአማርኛ ሚዲያዎቹ እንደሰበኩ ነው አማራው ግን ወደነሱ ጎራ አይገባም! ይህ መቀልበስ አለበት። በታሪክ ቁርሾዎች በግልጽ መነጋገር እና መስማማት ያስፈልጋል።  

Defensive መሆን አያስፈልግም። ለኢትዮጵያዊነት ተብሎ የሌሎችን ምልከታ በትህትና መቀበል አለብን። በነዚህ አካሄዶች የአማራ ልሂቃን እና ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር በተለይም ከለዘብተኞች ጋር ትብቅ ትስስር እንዲኖረን መስራት የግድ ነው።

ኢትዮጵያዊነት ከባድ ስራ እንደሆነ እንደሚሆን ግልጽ ነው። ግን ለአማራ ህዝብ የግድ ነው። ሌላ አማራጭ የለውም ታሪክ ይህንን ነው ያዘጋጀለት። ስለዚህ ወደ ስራ መግባት ነው እንጂ ስራን ሸሽቶ ወደ «የእጽ ፖለቲካ» የሆነው የአማራ ብሔርተኝነት መግባት የአማራ ህዝብ ሞት ንወ የሚሆነው።

Wednesday 2 November 2022

FUD

 Written February 2022


አንድ የፕሮፓጋንዳ ዘዴ Fear Uncertainty Doubt (FUD) ይባላል። የዚህ ዘዴ አላማ አንድ ህብረተሰብ በፍርሀት፤ በአለማረጋጋትና በጥርጣሬ መንፈስ እንዲሞላ ነው። የአንድ ህብረተሰብን ስነ ልቦና በዚህ መንፈስ ከተሞላ የገዛ ራሱን ሸባና አቅመ ቢስ ያደርጋል። ከዛ በቀላሉ ይገዛል።
በተለይ ከነጭና ቆይ ሽብር በሗላ በኢትዮጵያዊነት የሚያምነው ህብረተሰብ ስነ ልቦናው በፍርሀትና ጨለምተኝነት ተሞላ። ፖለቲካ ኮሬንቲ ነው ብሎ ከምንም አይነት መተባበርና መደራጀት ሸሸ። እንኳን በዘዴና በብልህነት በየዋሕነትም ለደህንነቱ መታገል አቃተው።
የዚህ ህብረተሰብ ጠላቶች ይህ ስነ ልቦናው ገብቷቸው ህብረተሰቡን በቀላሉ ለመግዛት FUD ፕሮፖጋንዳን ተጠቀሙ። ወደ ፍርሀት፤ አለመረጋጋትና ጥርጣሬ ያመዘነ ህዝብን ትንሽ ገፋ ካርግነው ወጥመድ ውስጥ ገብቶ ይቀራል ብለው አበቡ እንዳሉትም ሆነ።
የ FUD ዘዴ ቀልጣፋነት ዋናው ምክነያት የመቀጣጠል ባህሪው ነው። እንደ ቫይረስ ይሰራል። ይህ ማለት አንዴ ህብረተሰቡን ፍረሀት፤ አለሚጋጋትና ጥርጣሬን ካሳቀፍነው ህብረተሰቡ እራሱ እርስ በርሱ ፕሮፖጋንዳውን ያሰራጭል! የጠላት ስራ ይቀላል።
ባለፈው 30 ዓመት ዛሬም ይህ ነው በኢትዮጵያዊነት ጎራው ሲከሰት የታየው። ባለው በነባራዊው ሁኔታ ደስተኛ ያልሆኑት ንግግራቸው መልእክቶቻቸው አሉታዊ ናቸው። ከሌ እየጎዳን ነው፤ ከሀዲ ነው፤ እነሱ እየመጡብን ነው፤ ደህና ሰው የለም፤ አለቀልን ፤ ወዘተ። እነዚህ መልእክቶች የጠላትን የFUD ፕሮፓጋንዳ የሚያስፈጽሙ ናቸው። ህዝብን በቀላሉ እንዲገዛ የሚያደርጉ ናቸው።
ህብረተሰቡ ለራሱ ሰላም እንዲቆምና እንዲታገል የሚፈልጉ የFUD ተቃራኒ መልእክቶችን ነው ማስተላለፍ የለባቸው።
ቀጥታ ምሳሌ ልሰጣችሁ። ብልጽግና አማራንና ኢትዮጵያን አደጋ ላይ እየጣላት ነው ብለው የሚያምኑት ዛሬ ምንድነው የፕሮፖጋንዳ መልእክቶቻቸው ምንድ ነው መሆን ያለበት? ዛሬ ከሞላ ጎደል 100% መልእክቶቻቸው አሉታዊ ነወ፤ ባጭሩ "ብልጽግና የጠፋናል" ነው። የFUD መልእክት ነው ህዝቡ ተስፋ ቆርጦ ወደ ተግባር እንዳይሄድ ያደርገዋል። በተዋራኒው 100% መልእክቱ መሆን ያለበት ህብረት ፍጠር፤ ተደራጀ፤ እርስ በርስ ተዋወቅ፤ አንድ ሁን፤ ተዘጋጅ፤ ወዘተ። ይህ መልእክት የህዝቡን ስነ ልቦና ከተጽእኖ ተደራጊ ወደ ተግባረኛ ይቀይረዋል። ቤቱ ቁጭ ብሎ ከሚያዝን ወደ ራስ ማዳን ስራ እንዲገባ ይገፋፈዋል። ይህ ነው የሚፈለገው።
በግሌ መንግስት በጎብዝም ባይረባም በኢትዮጵያዊነት የሚያምነው ህብረተሰብ ወደ ስራ ካልገባና ካልተደራጀ ከባድ ጉዞ ነው የሚሆነው። በFUD የተጠመደ ህዝብ ለራሱ አደጋ ነው።

Tuesday 25 October 2022

የኩርፍያ ፖለቲካ

«እነ ስብሐት ነጋ ከተፈቱ ጀምሮ የአዲስ አበባ ህዝብ በዐቢይ ላይ አክሩፏል። ሮንድ ማድረርም አቆመ» ተባልኩኝ።

ይህ የፖለቲካችንን መሰረታዊ ችግር ያሚገልጽ አባባል ነው። ህዝቡ ማድረግ የነበረበት፤

1. ተቃውሞውን በሚገባው መግለጽ መንግስት እንዲሰማ እና እንዲገባው

2. እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይደገም የመንግስት ስራተኞች፤ ህዝብ ወኪሎች፤ መሪዎችን መወትወት

ይህን ከማድረግ ፋንታ ህዝቡ ምን አደረገ፤

1. መንግስትን በሚያዳክም መልኩ እና ጠላትን በሚያጎለብት መልኩ መንግስትን ተቸ!

2. አክሩፎ እንደ ህጻን እራሱን የሚጎዳ ድርጊቶች ፈጸመ፤ ለምሳሌ አካባቢውን መጠበቅ ተወ!

ለ45 ዓመት በላይ ፖለቲካ ያቃጠለው ህዝብ እንደዚህ የፖለቲካ ደንቆሮ ይሆናል። የመንግስትን እርምጃ ለመቃወም የራሱን ጥቅም ይጎዳል! አካባቢ መጠበቅ ሮንድ ማድረግ ህዝቡን እጅግ ጠቅሟል። ደህንነትን እና አብሮነትን ጨምሯል። ህዝቡ ለዚህ መስክሯል። ስለዚህ ለራሱ ጥቅም ብሎ እነዚህን ስራዎች መቀጠል ነበረበት። ይህ ሎጂካል ነው። ግን ይህን ከማድረግ መንግስትን አክሩፍያለው ብሎ እራሱን መጉዳት ጀመረ።

ህወሓት ይሁን ሌሎች በቀላል ወሬ በህዝባችን የሚጫወቱት ለዚህ ነው። አህያ የሚሉንም ለዚህ ነው። ፖለቲካ አይገባውም። የራሱን ጥቅም አያውቅም። በቀላሉ ከምነግስት ልናፋታው እንችላለን ነው እነ ህወሓት የሚያስቡት። እንሆ ለ27 ዓመት የገዛነው ደንቆሮ ስለሆነ ነው በይፋ የሚሉት።

ሀገራችን ሰላም እንዲኖራት ይህን ነገራችንን ማሻሻል አለብን። መንግስት እያንዳንዱን የፈለግኩት ነገርን ካላደረገ ይፍረስ የሚለውን የመሃይ አስተሳሰብ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን። ቀላል ዘመቻ አይሆንም።

Monday 24 October 2022

ስደተኛን መቀበድ፤ በጎነት ወይንም ጥቅም

የዋህ ስለሆንን የካናዳ መንግስት የህወሓትን መሪዎች በስደተኝነት ከተቀበለ ካናዳ እንዴት በጎ አገር ነው ብለን እናስባለን። የምዕራባውያን አገራት ፕሮፓጋንዳ በዓስለም ታሪክ አንደኛ መሆኑ የሚመሰክረው እንዴት ለራሳቸው ጥቅም የሚያደርጉትን ነገር እንደ በጎነት አድርገው የማሳየት እና ሌሎችን የማሳመን ችሎታቸው ነው!

አንድ አገር የሌአ እገር የተሰደደ መሪ የሚቀበለው ዋጋ ስለሚያገኝበት ነው። አንድ፤ ብዙ እውቀት እና ችሎታ ያለው ሰው ያገኛል። ይህ ሰው እውቀቱን፤ ሚስጠሮችን፤ ምክሮችን ለአዲስ ባለሟሎቹ ይሰጣል! ሁለት፤ የተቀባይ አገሩን «በጎነት» ፕሮፓጋንዳ ያስመሰክራል።

የህወሓት ያረጁ መሪዎች ለካናዳ ምን ይሰሩለታል ብላችሁ ትጠቅቁ ይሆናል? እኛ የዋሆች ነን እኮ እንደዚህ በአጭሩ የምናስበው። ብልሃት ያላቸው መንግስታት እያንዳንዱን ትንሽ ነገር ዋጋ ይሰጡታል ያጠራቅማሉም። ሁሉም አብሮ ሲደመር ትልቅ ክምችት ይሆናል።

ዓለም እንደዚህ ነው እውነቱ። በዚ በኩል የዋህ ባንሆን ይሻላ።